Telegram Group & Telegram Channel
"ርዕሱን ለአድማጭ"
ርዕሱ ነው
( አምባዬ ጌታነህ )

እኔ የአንቺ ደሐብ-ብኩን ደግ አፍቃሪ፣
ለክብረሽ መግለጫ - ፊደልሽን ቆጣሪ፣
እየተቅለሰለስኩ በልጅሽ ፊት ስኖር፣
ከማዘን በስተቀር ስቄ አላቅም ከምር።
ያም ለዛ ያም ለዛ ሲያጋድል እያየሁ፣
በጊዜ ዳኛ ላይ ፍትህ እየተራብሁ፣
ሁሌ እንዳጉተመተምሁ
'ልጅ አሳድግ ብየ
ካገር እኖር ብየ
ለባሻ ዳርኩለት ሚስቴን 'ህቴ ብየ።'
እንዳለው ገበሬ፣
አለሁኝ እንዳለሁ
ግፍ ሆኖብኝ ክብሬ።

አባት ማጣት ሀዘን - እናት ማጣት ህመም፣
ሆኖ እንደ እግር እሳት እልፍ አመት ቢፈጅም፣
በተበዳይ ልብ ውስጥ ለምፅ እንደሚያሳርፍ ገዳይ አውቆ አያቅም፣
እኔ ያለ ወላጅ መቅረቴ አያመውም።

ሰማይ የግፍ እምባ ሊጥል አቀርዝዟል፣
ጋራ ሸንተረሩ በዝምታ ነግሷል፣
ሜዳ ወንዛ ወንዙ ቅጠሉ ጠንዝሏል፣
እናት ሞቅ አጥልቃ፣
ቁርንጮዋን ታጥቃ፣
ፊቷ ተነጫጭቷል፣
አባት ወደ ማታ ባዘን አጎንብሷል፣
የእኔም የነገ እጣ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

ለዛሬ ያለምነው ቅዠት ሲሆን ተስፋ፣
አንተ የፍጥረት አምላክ
የምህረት ዝናብህን ባጥል እንኳ አካፋ።
ነፃ በሆነች ምድር ነፃ አውጪዎች ሞልተው ነፃ ህዝብ ጠፋ።
እኒህ ነፃ አውጪዎች
የለውጡ አምበሳዎች
በቀን አስር ጊዜ ' እመኑን 'የሚሉን፣
ከምናየው እውነት የተፃረረውን
' መሲህ ነን ' የሚሉን
ከእመኑን ባሻገር እንድናምን 'ሚሹት ውሸቱ ምን ይሆን፣

ባለሁለት ወንበር ምቾት ካልተሰማኝ፣
የምለውን ሰምቶ ሰርቶ ካልታዘዘኝ
አባወርነቴን ከተፈታተነኝ
የእሱ መኖር ለእኔ ..
መሄጃ መቆሚያ ማረፊያ ካሳጣኝ፣
እንዴት መላ አላስብ፣
እንዴት ሴራ አልሸርብ
የምን እያቀፉ እንደ ልጅ ማባበል፣
ሳለ ብልህ ዘዴ
በመፈንቅለ ስም መሪነትን መግደል።

እንዲህ ነው እንግዲህ የኛ ዘመን ጣጣ፣
የየዋህ እስትንፋስ የንፁህ እድል እጣ።
ያደለው በሰው ልብ እንደተናፈቀ በክብር ይሞታል፣
ያለደለው ደግሞ የራሱን ቁም ሙቶ ሊገድል ይኖራል፣
ምንድን ነው ሰው መሆን ያዘነ ማስመሰል፣
በውስጥ እየሳቁ ለቅሶ ምን ያደርጋል፣
ፍረድ አንተ ጌታ...
የኃጢያት እልፍኜን
ና ደብድብ ጣራዋን
ወየ ኡኡ ብየ ላቅልጠው ዋይታየን
ቅጣኝ ለክህደቴ
አርገው እውነት የምር የውሸት ለቅሶየን።

እናም በኔ ዘመን...
የእውነት ዘውድ ተጭኖ የሚታየው አሁን፣
ቀዳዳን በር አረጎ ሚያይ ልዩነትን
አንድነትን ትቶ የሚስብክ ጥልን።
በአንድ መንጋ ሚሄድ፣
ያለ ሀሳብ ሚነጉድ
ግን
እስከየት ድረስ ነው?
ጎዳናው ሚያዘልቀው
እስከ መቼ ድረስ በጎጥ አንድ መንገድ፣
በንፁሃን ደም ላይ..
ንፁሃንን ከሶ እያሰሩ መሄድ።
ነውስ?
'ውሻ በቀደደው ጅብ ሠፍቶ ይገባል
ፍየል በግ ቢያጣ እንኳ
ቋንጣውን ሸምጥጦ ይሮጣል እንዲባል
ሆነ በቃ እንግዲህ
የዚች አገር እጣ በተራ መበደል?!

ተው
እንተው
በዳይ ከተበዳይ እኩል ፍትህ ካለ ካልሰከነ ነገር፣
ቤትን ካላቆመ
አንደኛው ጭራሮ ሌላው ሆኖ ማገር፣
ምስጥ የበላት ጎጆ ትመስላለች ሀገር።
"
' ? '
በበረሀ ጋመን ጠውልጎ ያልረባው፣ማውጣት የተሳነው የማህፀንሽ ፍሬ፣
ለአርባ አምስት አመታት ንጉሥ ያልወጣብሽ ምን ኀጥያት ሰርተሽ ነው ንገሪኝ ሀገሬ?

ምንዱባን ኢትዮጵያ - ምትለምኝ ሰጥተሽ፣
ጥበብሽ ሳይቆሽሽ
የምታጥቢ ፈተሽ
ሩህሩኋ የኔ
ጥጥ ፈታይዋ እናቴ፣
ምን ልብ ነው ያለሽ
እኔ እየጠላሁሽ
አንቺ ምትሳሽልኝ ንገሪኝ በሞቴ?

' መደምደሚያ '
በአንድ ቋንቋ ዘየ የሰራነው መንደር፣
ምን ብንኩራራበት አይሆነንም ሀገር።
ይብቃን መጋደሉ፣
ይብቃን መላቀሱ፣
መርገምት ነው ይሄ
እንፀልይ ወደ እርሱ።
ደግሞ
ያሻው ቢከፋኝም፣
ያሻ ብቀየምም፣
ወንድምነትክን ግን
ለሰከንድ አልፍቅም
ሲነኩህ ያመኛል ይሰማዋል ጎኔ፣
ይህ ሁሉ ግፍ ይቁም በአንተ በእሷ በእኔ
ልዩነቱ ይብቃን አንድ እንሁን ወገኔ።


ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@Getemlemitemaw
@Getem_lemitemaw
@Getemlemitemaw



tg-me.com/Getem_lemitemaw/632
Create:
Last Update:

"ርዕሱን ለአድማጭ"
ርዕሱ ነው
( አምባዬ ጌታነህ )

እኔ የአንቺ ደሐብ-ብኩን ደግ አፍቃሪ፣
ለክብረሽ መግለጫ - ፊደልሽን ቆጣሪ፣
እየተቅለሰለስኩ በልጅሽ ፊት ስኖር፣
ከማዘን በስተቀር ስቄ አላቅም ከምር።
ያም ለዛ ያም ለዛ ሲያጋድል እያየሁ፣
በጊዜ ዳኛ ላይ ፍትህ እየተራብሁ፣
ሁሌ እንዳጉተመተምሁ
'ልጅ አሳድግ ብየ
ካገር እኖር ብየ
ለባሻ ዳርኩለት ሚስቴን 'ህቴ ብየ።'
እንዳለው ገበሬ፣
አለሁኝ እንዳለሁ
ግፍ ሆኖብኝ ክብሬ።

አባት ማጣት ሀዘን - እናት ማጣት ህመም፣
ሆኖ እንደ እግር እሳት እልፍ አመት ቢፈጅም፣
በተበዳይ ልብ ውስጥ ለምፅ እንደሚያሳርፍ ገዳይ አውቆ አያቅም፣
እኔ ያለ ወላጅ መቅረቴ አያመውም።

ሰማይ የግፍ እምባ ሊጥል አቀርዝዟል፣
ጋራ ሸንተረሩ በዝምታ ነግሷል፣
ሜዳ ወንዛ ወንዙ ቅጠሉ ጠንዝሏል፣
እናት ሞቅ አጥልቃ፣
ቁርንጮዋን ታጥቃ፣
ፊቷ ተነጫጭቷል፣
አባት ወደ ማታ ባዘን አጎንብሷል፣
የእኔም የነገ እጣ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

ለዛሬ ያለምነው ቅዠት ሲሆን ተስፋ፣
አንተ የፍጥረት አምላክ
የምህረት ዝናብህን ባጥል እንኳ አካፋ።
ነፃ በሆነች ምድር ነፃ አውጪዎች ሞልተው ነፃ ህዝብ ጠፋ።
እኒህ ነፃ አውጪዎች
የለውጡ አምበሳዎች
በቀን አስር ጊዜ ' እመኑን 'የሚሉን፣
ከምናየው እውነት የተፃረረውን
' መሲህ ነን ' የሚሉን
ከእመኑን ባሻገር እንድናምን 'ሚሹት ውሸቱ ምን ይሆን፣

ባለሁለት ወንበር ምቾት ካልተሰማኝ፣
የምለውን ሰምቶ ሰርቶ ካልታዘዘኝ
አባወርነቴን ከተፈታተነኝ
የእሱ መኖር ለእኔ ..
መሄጃ መቆሚያ ማረፊያ ካሳጣኝ፣
እንዴት መላ አላስብ፣
እንዴት ሴራ አልሸርብ
የምን እያቀፉ እንደ ልጅ ማባበል፣
ሳለ ብልህ ዘዴ
በመፈንቅለ ስም መሪነትን መግደል።

እንዲህ ነው እንግዲህ የኛ ዘመን ጣጣ፣
የየዋህ እስትንፋስ የንፁህ እድል እጣ።
ያደለው በሰው ልብ እንደተናፈቀ በክብር ይሞታል፣
ያለደለው ደግሞ የራሱን ቁም ሙቶ ሊገድል ይኖራል፣
ምንድን ነው ሰው መሆን ያዘነ ማስመሰል፣
በውስጥ እየሳቁ ለቅሶ ምን ያደርጋል፣
ፍረድ አንተ ጌታ...
የኃጢያት እልፍኜን
ና ደብድብ ጣራዋን
ወየ ኡኡ ብየ ላቅልጠው ዋይታየን
ቅጣኝ ለክህደቴ
አርገው እውነት የምር የውሸት ለቅሶየን።

እናም በኔ ዘመን...
የእውነት ዘውድ ተጭኖ የሚታየው አሁን፣
ቀዳዳን በር አረጎ ሚያይ ልዩነትን
አንድነትን ትቶ የሚስብክ ጥልን።
በአንድ መንጋ ሚሄድ፣
ያለ ሀሳብ ሚነጉድ
ግን
እስከየት ድረስ ነው?
ጎዳናው ሚያዘልቀው
እስከ መቼ ድረስ በጎጥ አንድ መንገድ፣
በንፁሃን ደም ላይ..
ንፁሃንን ከሶ እያሰሩ መሄድ።
ነውስ?
'ውሻ በቀደደው ጅብ ሠፍቶ ይገባል
ፍየል በግ ቢያጣ እንኳ
ቋንጣውን ሸምጥጦ ይሮጣል እንዲባል
ሆነ በቃ እንግዲህ
የዚች አገር እጣ በተራ መበደል?!

ተው
እንተው
በዳይ ከተበዳይ እኩል ፍትህ ካለ ካልሰከነ ነገር፣
ቤትን ካላቆመ
አንደኛው ጭራሮ ሌላው ሆኖ ማገር፣
ምስጥ የበላት ጎጆ ትመስላለች ሀገር።
"
' ? '
በበረሀ ጋመን ጠውልጎ ያልረባው፣ማውጣት የተሳነው የማህፀንሽ ፍሬ፣
ለአርባ አምስት አመታት ንጉሥ ያልወጣብሽ ምን ኀጥያት ሰርተሽ ነው ንገሪኝ ሀገሬ?

ምንዱባን ኢትዮጵያ - ምትለምኝ ሰጥተሽ፣
ጥበብሽ ሳይቆሽሽ
የምታጥቢ ፈተሽ
ሩህሩኋ የኔ
ጥጥ ፈታይዋ እናቴ፣
ምን ልብ ነው ያለሽ
እኔ እየጠላሁሽ
አንቺ ምትሳሽልኝ ንገሪኝ በሞቴ?

' መደምደሚያ '
በአንድ ቋንቋ ዘየ የሰራነው መንደር፣
ምን ብንኩራራበት አይሆነንም ሀገር።
ይብቃን መጋደሉ፣
ይብቃን መላቀሱ፣
መርገምት ነው ይሄ
እንፀልይ ወደ እርሱ።
ደግሞ
ያሻው ቢከፋኝም፣
ያሻ ብቀየምም፣
ወንድምነትክን ግን
ለሰከንድ አልፍቅም
ሲነኩህ ያመኛል ይሰማዋል ጎኔ፣
ይህ ሁሉ ግፍ ይቁም በአንተ በእሷ በእኔ
ልዩነቱ ይብቃን አንድ እንሁን ወገኔ።


ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@Getemlemitemaw
@Getem_lemitemaw
@Getemlemitemaw

BY ግጥም ለሚጠማዉ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/Getem_lemitemaw/632

View MORE
Open in Telegram


ግጥም ለሚጠማዉ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

To pay the bills, Mr. Durov is issuing investors $1 billion to $1.5 billion of company debt, with the promise of discounted equity if the company eventually goes public, the people briefed on the plans said. He has also announced plans to start selling ads in public Telegram channels as soon as later this year, as well as offering other premium services for businesses and users.

Telegram Auto-Delete Messages in Any Chat

Some messages aren’t supposed to last forever. There are some Telegram groups and conversations where it’s best if messages are automatically deleted in a day or a week. Here’s how to auto-delete messages in any Telegram chat. You can enable the auto-delete feature on a per-chat basis. It works for both one-on-one conversations and group chats. Previously, you needed to use the Secret Chat feature to automatically delete messages after a set time. At the time of writing, you can choose to automatically delete messages after a day or a week. Telegram starts the timer once they are sent, not after they are read. This won’t affect the messages that were sent before enabling the feature.

ግጥም ለሚጠማዉ from sa


Telegram ግጥም ለሚጠማዉ
FROM USA